Konso Zone
Higher Officials
የኮንሶ ዞን መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
“የመንግስት ኮሚኒኬሽን፧- አንድ ለብዙ፣ የህዝብ አይንና ጆሮ ነው!”
ኮንሶ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ በመንግስት እና ህዝብ መካከል በመሆን መረጃን የማስተዳደር፣ የማሰባሰብና የማሰራጨት ሃላፊነት አለው።
ኮሚኒኬሽን መምሪያ የመንግስት ፖሊሲዎችን፣ ፕሮግራሞችን፣ ዕቅዶችን እና ተነሳሽነቶችን ለዜጎች በማሳወቅ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ኮንሶ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የስራ ቢጋር፡-
1. ግልፀኝነት፡- የኮንሶ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የመንግስት ተግባራትን፣ ፖሊሲዎችን እና ውሳኔዎችን ለህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት ግልፅነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሚሰራ የህዝብ አይንና ጆሮ ነው።
2. የህዝብ ግንኙነት፡- መሥሪያ ቤቱ ከሕዝብ ጋር በንቃት በመነጋገርና የሚነሱ ችግሮችንና ትችቶችን በመፍታት የመንግሥትን እና የሕዝብ ህልውናን በበይነ መረብና ብዙኃን መገናኛ የሚያሰራጭ መንግስታዊና ህዝባዊ አደራ ያለበት ተቋም ነው።
3. የሚዲያ ግንኙነት፡- የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር ያላቸውን ግንኙነት በመጠበቅ ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ለማድረስ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር፣ ሚዲያ ተቋማትን የሚመራ፣ መረጃ የሚያቀብል “አንድ ለብዙ!” የሆነ የህዝብና የመንግስት ተቋም ነው።
4. ትምህርት እና ግንዛቤ፡- መሥሪያ ቤቱ ስለ መንግሥት ፕሮግራሞች፣ አገልግሎቶች እና የዜጎች ግንዛቤን ለማሳደግ ህብረተሰቡን በሚገባው ቅርብ ቋንቋ ለማስተማር በንቃት የሚሰራ መምሪያ ነው።
5. መስተጋብር፡- የመንግስት ኮንሶ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ከህዝቡ ጋር በመሰናሰል ግብረ መልስ መረጃዎችን የሚሰበስብና የሚያሰራጭ፥ ለጥያቄዎች ከጉዳዩ ባለቤቶች ጋር በመተባበር ምላሽ የሚሰጥ እና በመንግስት እና በዜጎች መካከል ሰላማዊ ድልድይ እንዲፈጠር የሚሰራ አንዱ ለሁሉ የሚሰራ ተቋም ነው።
በአጠቃላይ ኮንሶ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ በመንግስት እና በህዝብ መካከል ውጤታማ ግንኙነትን በማመቻቸት ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
መሥሪያ ቤቱ በመረጃ ግብዓት የዜጎን ንቃቴ ህሊና ለማሳደግ የሚሰራ፣ ሰላማዊ ግንኙነት እንዲኖር የሚተጋና የሚያስተባብር አሳታፊ ዴሞክራሲያዊ፣ ማህበረኣዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፓለቲካዊ እና ባህላዊ ስርዓት እንዲጎለብት የበኩሉን አስተዋፅዖ እያበረከተ ያለ የህዝብ አይን እና ጆሮ ነው።
አቶ ሠራዊት ዲባባ
የኮንሶ ዞን መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ ኃላፊ
- Phone:+046 773 0635
- Email:konsocommunication.com
አቶ መሳይ አሰፋ
የኮንሶ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ
We are working on it please wait .....
- Phone:+2519
- Email:working on it